የሽግግር ፍትሕ በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ በተለያዩ የታሪክ አጋጣሚዎች የተፈጠሩ የፍትሕ መጓደሎችን እና መሰረታዊ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በመመርመር አጥፊዎችን በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ፣ ተጎጂዎች መልሰው የሚቋቋሙበት እና ካሳ የሚያገኙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እንዲሁም በአጠቃላይ በሀገራችን የተለያዩ የታሪክ ምዕራፎች የተፈጸሙ በደሎችን አስመልክቶ እውነትን በማፈላለግ በእውነት እና በይቅርታ ላይ የተመሰረተ እርቅን በማምጣት ሀገራችንን ከሚፈታተናት የግጭት አዙሪት ለማውጣት ይቻል ዘንድ የኢትዮጵያ ፌዴራልዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት በጥቅምት ወር 2015 .ም የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ዝግጅትን በይፋ አስጀምሯል።

በኢትዮጵያ በተለያዩ የታሪክ አጋጣሚዎች የተፈጠሩ የፍትሕ መጓደሎችን እና መሰረታዊ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በመመርመር አጥፊዎችን በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ፣ ተጎጂዎች መልሰው የሚቋቋሙበት እና ካሳ የሚያገኙበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እንዲሁም በአጠቃላይ በሀገራችን የተለያዩ የታሪክ ምዕራፎች የተፈጸሙ በደሎችን አስመልክቶ እውነትን በማፈላለግ በእውነት እና በይቅርታ ላይ የተመሰረተ እርቅን በማምጣት ሀገራችንን ከሚፈታተናት የግጭት አዙሪት ለማውጣት ይቻል ዘንድ የኢትዮጵያ ፌዴራልዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት በጥቅምት ወር 2015 .ም የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ዝግጅትን በይፋ አስጀምሯል።

የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ዝግጅቱ ገለልተኛ በሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን፣ የሕግ ባለሙያዎችን እና በተለይም በሽግግር ፍትሕ ረገድ ልዩ የከፍተኛ ትምህርት ዝግጅት ባላቸው ባለሙያዎች አማካንነት በፍትሕ ሚኒስቴር አስተባባሪነት ተዘጋጅቷል። ረቂቅ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ ሰነዱ ላይ በመላ ሀገሪቱ 80 ሕዝባዊ መድረኮች ተዘጋጅተው ውይይት የተደረገበት ሲሆን በእነኚህ መድረኮች ላይ 4800 የሚሆኑየህብረተሰበተወካዮች፣ተጎጂዎች፣የመንግስትየስራኃላፊዎች፣የሲቪልማህበረሰብተወካዮች፣በሽግግርፍትሕዙሪያአለምአቀፍኤክሰፐርቶችእናየዲፕሎማቲክማህበረሰብተሳትፈውባቸዋል።

በዚህ አሳታፊ ሂደት ያለፈው የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ዝግጅት ከተደረጉት መድረኮች በተገኙ ግብዓቶች ዳብሮ ሚያዚያ 8 ቀን 2016 .ም በኢ...ሪየሚኒስትሮችምክርቤትጸድቋል።

የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲው በውስጡ፡-

  • የወንጀል ተጠያቂነትን፣
  • እውነት የማፈላለግን፣ ይፋ የማውጣትን እና የዕርቅ ተግባርን፣
  • በቅድመሁኔታ ላይ ሰለሚመሰረት ምህረት፣
  • የማካካሻ ስርዓትን እና
  • ተቋመዊማሻሻያን

የሚመለከቱ ዝርዝር አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

እነኚህንም አቅጣጫዎች በመከተል ፖሊሲውን ለማስፈጸም የሚረዱ ሕጎችን የማርቀቅ ስራ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን እነኚህም፡

  • የልዩ ዐቃቤ ሕግ ጽ/ቤትን፣ የእውነት ኮሚሽንን እና የማጥራት ኮሚሽንን ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ በመድብል
  • የዓለም አቀፍ ወንጀሎች ረቂቅ አዋጅ እና
  • የልዩ ችሎት ማቋቋሚያ ረቂቅ አዋጅ ናቸው።

የእነኚህን ሕጎች ረቂቅ የማዘጋጀት ስራው ፖሊሲውን ባዘጋጀው ገለልተኛ የባለሙያዎች የስራ ቡድን የተከናወነ ሲሆን የረቂቅ ሕጎቹ ዝግጅት ሲጠናቀቅ ፖሊሲው በጸደቀበት የአካሄድ አግባብ ሰፊ በሆነ ሕዝባዊ ምክክር እንዲያልፍ በማድረግ ከምክክሩ የሚገኙ ገንቢ ግብዓቶች እንዲካተቱበት የሚደረግ ይሆናል።

ዋና ዋና ተግባራት

የሕግ እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች

የፍትሕ ዘርፍ ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ

ዜና

የጀርመን የልማት ተራድኦ ድርጅት በኢትዮጵያ (GIZ) ኢትዮጵያ የፌደራል አስተዳዳር ስነ-ሥርዓት ሕግ አፈፃፀም እና የሰብዓዊ መብት ክትትልን ለማሳደግ እንዲሁም የሽግግር ፍትሕን ለመተግበር የሚያግዙ የሰነድ እና ቁሳቁስ ድጋፍ አበረከተ • GIZ Ethiopia Supports Implementation of Federal Administrative Law, Human Rights Monitoring, and Transitional Justice

የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሀና አርዓያ ስላሴ መቀመጫቸውን ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ላደረጉ አምባሳደሮች እና የዓለም ዐቀፍ ተቋማት ተወካዮች በሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ትግበራ ምዕራፍ ዙሪያ ገለጻ አቀረቡ • Ethiopian Minister of Justice, H.E. Hanna Araya Selassie, Addresses Ambassadors and International Organization Representatives on Transitional Justice Policy Implementation Process

የፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ በላይሁን ይርጋ ከተባበሩት መንግስታት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ምክትል ተወካይ እና የኢትዮጵያ ፕሮግራም ኃላፊ ከሆኑት ሚስተር ቻርለስ ኩዌሞይ ጋር ተወያዩ • Minister of State Belayhun Yirga Discusses Cooperation with UN Deputy High Commissioner for Human Rights Representative, Charles Kuwomoi

“የአገራችንን ሁለንተናዊ እድገት ለማስቀጠልና ብልፅግናን እዉን ለማድረግ ቁልፍ መሳሪያችን ለጋራ ዓላማ በጋራ መቆም ነዉ፤ ለዚህ ደግሞ አገራዊ ሰላምን ማስፈንና የሕግ የበላይነትን ማረጋገጥ የቅድሚያም ቅድሚያ የሚሰጣቸዉ ቁልፍ ስራዎች ይሆናሉ!” ክቡር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ • “Our Key Instrument to Sustain Our Country’s Holistic Development and Realize Prosperity is to Stand Together for a Common Goal; To This End, Ensuring National Peace and Upholding the Rule of Law Will Be Paramount Priorities!” Honorable President of the FDRE, Ambassador Taye Atske Selassie

ጋዜጣዊ መግለጫዎች

ጽሑፎች

ቪዲዮዎች