ኢትዮ-ኮሎምቢያ የሽግግር ፍትሕ እና የሰላም ባህል የልምድ ልውውጥ ተካሄደ

Ethiopia and Colombia Sharing Experience on Transitional Justice and the Culture of Peace

በኢትዮጵያና በኮሎምቢያ መካከል ትኩረቱን የሽግግር ፍትሕ እና የሰላም ባህል ላይ ያደረገ ዓለም ዓቀፍ ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን በዚሁ ወቅት ሁለቱ አገራት ያላቸውን ልምድ በማጋራት የልምድ ልውውጥ አድርገዋል።

የሰላም እጦት ጉዳይ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለፓለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት ተግዳሮት እየሆነ ያለ ጉዳይ መሆኑ እና ለዚህም ሁሉም አካላት ሰላምን ባህል ለማድረግ በየ ጊዜው መሰል የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት መነጋገር እንዳለባቸው የተገለፀ ሲሆን አገራት በተናጠል ከሚያከናውኗቸው ተግባራት በተጨማሪ በጋራና በትብብር መስራት እንደሚገባቸው ተመላክቷል።

በተጨማሪም የሽግግር ፍትሕ በመተግበር ሂደት ውስጥ ኮሎምቢያ የተጓዘችበት መንገድ እና የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ የሚገኙ በባህሪ ተቀራራቢ በመሆናቸው የሁለቱን ሀገራት ልምድ ለመቀመር የሚያስችል የልምድ ልውውጦች የሚኖራቸውን ጠቀሜታ የጎላ እንደሚያደርገው ተገልጿል።

በመድረኩ በኢትዮጵያ በኩል፣ በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ሂደት የሰብዓዊ መብት ተቋማት እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም የግብረ ሠናይ ድርጅቶች ሚና በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ገለጻ የቀረበ ሲሆን በኮሎምቢያ በኩል እንዲሁ የሰላም ባህልና የሽግግር ፍትሕ ትግበራ ዙሪያ ሰፋፊ ማብራሪያዎች ቀርበው ውይይቶች ተካሂደዋል።

ኮንፈረንሱን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር፣ በኢትዬጵያ የኮሎምቢያ ኤምባሲ እና የኢትዮጵያ የሕግ ትምህርት ቤቶች ማህበር በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን ፓሊሲ አውጭዎች፣ ዲፕሎማት፣ የዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች፣ የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅት ተወካዬች እና ሌሎች የዘርፉ ምሁራን ተሳትፈውበታል።

Tagged Under: african charter on the rights and welfare of the child and healthcare administration and control authority arts and culture constitution of the federal democratic republic of ethiopia Convention on the Rights of the Child convention on the rights of the child (crc) culture ethiopia revenue and customs authority experience Experience Sharing federal institute of justice and law federal justice and law institute government law and justice services sector international peace and security Justice justice and democracy affairs justice and law institute Justice For All - PF Ethiopia justice for all prison fellowship ethiopia medicine and healthcare administration and control authority medicine and healthcare administration and control proclamation no. 661/2009 pea peace per ring sharing transit transition transitional transitional justice
የቅርብ ጊዜ ዜናዎች

ተመሳሳይ ዜናዎች