የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ የማስፈጸሚያ ፍኖተ ካርታ ረቂቅ ላይ የግብዓት ጥሪ

Call for Input on the Draft Roadmap for the Implementation of the FDRE Transitional Justice Policy

የኢፌዲሪ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ወደ ትግበራ ምዕራፍ መሻገሩ ይታወቃል፡፡ የፍትሕ ሚኒስቴርም በፖሊሲው የተጣለበትን የማስተባበር ኃላፊነት ለመወጣት ያስችለው ዘንድ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ባሳተፈ መልኩ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲው የትግበራ ምዕራፍ የሚመራበትን ፍኖተ ካርታ ረቂቅ ሰነድ የማዘጋጀት ስራ አጠናቋል፡፡ በሚቀጥሉት ቀናትም በተዘጋጀው ረቂቅ ፍኖተ ካርታ ላይ የግብዓት ማሰባሰቢያ የምክክር መድረኮች ይካሄዳሉ፡፡ በመድረኮቹ የሚነሱ አስተያየቶችን በማካተት የመጨረሻው ሰነድ በተለያዩ ዘዴዎች ለመላው ሕዝብ የሚጋራ ሲሆን የማስግበሪያ ፍኖተ ካርታው በአጭር ጊዜ ውስጥም በተሟላ ሁኔታ ወደ ትግበራ እንደሚገባ ይጠበቃል፡፡

በመሆኑም ከዚህ መረጃ ጋር ተያይዞ በቀረበው ረቂቅ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ማስተግበሪያ ፍኖተ ካርታ ላይ አስተያየት ለመስጠት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው አስተያየቱን በኢሜይል አድራሻ [email protected] ላይ መላክ የሚችል መሆኑን በአክብሮት እየገለፅን፣ ረቂቅ የፍኖተ ካርታውን ከዚህ በታች የተጠቀሰውን ሊንክ በመጫን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

https://drive.google.com/…/1YaS9cqGvtlu9UraS83X…/view…

Relevant Departments and People
Tagged Under: Amhara civil Civil Society Organizations Consultation draft draft roadmap feedback Implementation input Justice legal framework Nationalities Nations organizations oromo peoples' Policy public Public consultation roadmap society southern southern nations stakeholder Stakeholder Consultation Tigray transitional transitional justice
የቅርብ ጊዜ ዜናዎች

ተመሳሳይ ዜናዎች