ይሕ ዳይሬክቶሬት በፍትሕ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ ሥር በሚገኙ በአዲስ አበባ፣ በድሬዳዋ እና በሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች የሚከናወኑ ተግባራትን ማስተባበር፣ መምራት፣ አፈፃፀማቸውን መገምገም፣መመዘን፣ግብረ መልስ መስጠት፣ወጥ አሠራር መዘርጋት፣ የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ኃላፊዎች የስራ አፈጻጸም መገምገም፣ መመዘን፣ግብረመልስ መስጠት፣ በቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች በሚሰጡ ውሳኔዎች ላይ የሚቀርቡ አቤቱታና እና ቅሬታዎችን ሰንሰለቱን ጠብቀው መቅረባቸውን ማረጋገጥ፣ ተቀብሎ ማስተናገድ፣ ውሳኔ መስጠት፣ አፈፃፀሙን መከታተል፣ በቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ሥልጣን ስር የሚወድቁ ሆነው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚቀርቡ የወንጀል ክሶችን ማቅረብና መከራከር፣ በቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች መካከል ሊኖር የሚገባውን ትስስርና መስተጋብር ሥርዓት መዘርጋት፣ ማቀናጀት፣ መምራት፣ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን የቅንጅታዊ አሠራር ሁኔታ ማስተባበር ከተሰጡት ኃላፊነቶች ዋና ዋናዎቹ ናቸው።











