ጌቱ ታደሰ ከበደ

ዳይሬክተር
ከመስከረም 2015 ዓ.ም ጀምሮ

ጌቱ ታደሰ ከመስከረም 2015 ዓ.ም ጀምሮ የቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች መከታተያ ዳይሬክቶሬትን በመምራት ላይ ይገኛል። በእርሱ አመራር የስራ ክፍሉ በተሳካ ሁኔታ በተቋሙ ስር የሚገኙ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶችን በመምራት፣ በመደገፍ እና በመከታተል፣ በቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ስልጣን ስር የሚወድቁ እና በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚቀርቡ የወንጀል ጉዳዮች ክርክርን በመምራት፣ በቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች የሚሰጡ ውሳኔዎች ላይ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ተቀብሎ የሚያስተናግድ እና ውሳኔ አሰጣጥን የሚመራ እና የሚወስን ሲሆን በዚህም ስራ ክፍሉ የተጣለበትን ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጣ አስችሏል። ኃላፊው በማስተባበር ክህሎቱ፣ በየትኛውም ደረጃ ከሚገኙ ኃላፊዎች፣ የፍትሕ አካላት ባለሙያዎች እና ኃላፊዎች እንዲሁም ከባለድርሻ አካላት ጋር አብሮ በመስራት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ ስር በሚገኙ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እየተከናወነ ካለውና እየጨመረ ከመጣው የሥራ ፍሰት አንጻር የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን ተግባራት አቀናጅቶ በመምራት፣ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ እና የቅርብ አመራር በመስጠት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቹ ውጤታማ ተግባር እንዲያከናውኑ በማስቻል  ስኬታማ ነው። አሁን ካለበት የአመራርነት  ተልዕኮ አስቀድሞ በዐቃቤ ሕግነት፣ በልዩ ልዩ ወንጀሎች ቡድን መሪነት እንዲሁም በቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ዋና ኃላፊነት ሲያገለግል የቆየ ሲሆን በዋናነት የምርመራ እና የክርክር ስራዎችን የመምራት ስራ ላይ ለረጅም ጊዜ ሰርቷል። ጌቱ ለ13 አመታት ያካበተውን የስራ ልምድ በመጠቀም የወንጀል ፍትሕ አስተዳደሩን በብቃት በመምራት እና ተቋም በመገንባት ኃላፊነቱን ለመወጣት ዝግጁ ነው።

የትምህርት ዳራ

  • ጎንደር ዩኒቨርስቲ፣ የሕግ ዲግሪ
  • የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ(የህግ ሁለተኛ ዲግሪ፣ በስራ አመራር ሁለተኛ ዲግሪ)

ዜና