የተቀናጀ፣ በተጠያቂነት ላይ የተመሠረተና ያልተማከለ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት በየደረጃው ከአደጋ በፊት፣ በአደጋ ጊዜና ከአደጋ በኋላ መወሰድ የሚገባቸውን ተገቢ እርምጃዎች በወቅቱና በየደረጃው በተሟላ ሁኔታ እንዲወሰዱ ማድረግ በማስፈለጉ፤
የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራርን ተግባራዊ በማድረግ በአደጋ ምክንያት ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የሚመለከታቸውን አካላት ሁሉ ለማሳተፍ በሕግ ማዕቀፍ መደገፍ በማስፈለጉ፤
በዋናነት ድርቅ ተኮርና አደጋ ከተከሰተ በኋላ የአስቸኳይ ጊዜ የዕለት ዕርዳታ በማቅረብ ሕይወት ማዳን ሥራ ላይ ያተኩር የነበረውን የአደጋ ሥራ አመራር አሠራር ወደ ተሟላ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር አሠራር ማሸጋገር በማስፈለጉ፤
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 916/2008 አንቀፅ 5 እና 39 መሠረት ይህንን ደንብ አውጥቷል፡፡
•
•
•
•
•
•
•
•
•
•