የኦዲት ሥርዓትን ማጠናከር መንግሥት የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በሚገባ ለመምራትና ለማስተዳደር የሚያስፈልገውን አስተማማኝ መረጃ በማግኘት ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያለው በመሆኑ፤
የፌዴራል መንግሥት ድርጅቶች፣ ኘሮጀክቶችና ኘሮግራሞች የገንዘብ አስተዳደር ተገቢውን የሂሣብ አያያዝ ስርዓት የተከተለ፤ የገቢ አሰባሰባቸው፣ የወጪ አፈቃቀዳቸውና የንብረት አስተዳደራቸው ተገቢውን ሕግና መመሪያ ተከትሎ የተፈፀመ መሆኑን ማረጋገጥ አስፈላጊ በመሆኑ፤
ከተጠቀሱት ድርጅቶች በተጨማሪ የፌዴራል መንግሥት የሕዝብ ጥቅም ተነክቷል ብሎ በማመኑ ምክንያት የሌሎች ድርጅቶች ወይም ኩባንያዎች የሂሣብ አሠራር ኦዲት እንዲደረግ በሚወስንበት ጊዜ ይህንን የኦዲት ሥራ የሚያከናውን ገለልተኛ የኦዲት ተቋም ማቋቋምና ማጠናከር አስፈላጊ በመሆኑ፤
ለዚሁም ዓላማ ከዚህ ቀደም በአዋጅ ቁጥር 126/1969 ዓ.ም ተቋቁሞ የነበረውን የሒሳብ ምርመራ አገልግሎት ድርጅት እንደገና ማቋቋም አስፈላጊ በመሆኑ፤
የፌደራል ዋናው ኦዲተር መሥሪያ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅን እንደገና ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 982/2ሺ8 አንቀጽ 5 እና የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 2ሺ11 አንቀጽ 2 ንዑስ አንቀጽ (17) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የሚከተለው ተደንግጓል፡፡
•
•
•
•
•
•
•
•
•
•