የፌዴራል ፖሊስ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥትንና ሕገ-መንግሥቱን መሠረት አድርገው የሚወጡ ሕጎችን የማስ ከበር ተልዕኮውን በብቃት በመወጣት የዲሞክራሲ ሥርዓትን ለመገንባት፣ ሠላምን ለማስፈንና ልማትን ለማፋጠን በሚደረገው ሀገራዊ እንቅስቃሴ የበኩሉን ድርሻ ለማበርከት እንዲችል በተሻለ ሁኔታ እንዲደራጅ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
የፌዴራል ፖሊስ ተቋም ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ገለልተኛ የሆነ፣ ሕብረተሰቡን በእኩልነት የሚያገለግል፣ በፖሊሳዊ ሥነ-ምግባሩ የታነፀና ብቃትና ጥራት ያለው አገልግሎት ሊሰጥ የሚችል ተቋም መሆኑን ማረጋገጥ አስፈላጊ በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•
•
•
•
•