በመሥሪያ ቤቱ ማቋቋሚያ አዋጅ አንቀጽ ፮(፪) ስር በግልጽ እንደተመለከተው መሥሪያ ቤቱ ተጠሪነቱ በቀጥታ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በመሆኑ የራሱ የሠራተኞች አስተዳደር ደንብ ማውጣት በማስፈለጉ፤
የፌደራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት እና በማቋቋሚያ አዋጁ ሥልጣንና ተግባራት ለማከናወን እንዲችል ሠራተኞችን ደንብና ሥርዓትን በተከተለ ሁኔታ ለመቅጠር፣ ለማስተዳደርና አስፈላጊ ሲሆን ለማሰናበት የሚያስችል የሠራተኞች አስተዳደርና ደንብ ማውጣት በማስፈለጉ፤
የመሥሪያ ቤቱ ሠራተኞች ሙያዊ ነፃነታቸውን ፣ መብትና ግዴታቸውን በውል ለይተው በማወቅ ተግባራቸውንና
ኃላፊነታቸውን ግልጽነትና ተጠያቂነት በሰፈነበት ሁኔታ መወጣት እንዲችሉ ለማገዝ፤
በተለይም መሥሪያ ቤቱ ባለው ሙያዊ ነፃነት መሠረት ከአህጉራችንና ከዓለም አቀፍ የኦዲት መ/ቤቶች
ሠራተኞቻቸውን የሚያስተዳድሩበትን ልምድ በመቀመር እና የፌደራል የመንግሥት ሠራተኞች አዋጅ መሠረታዊ ርሆዎች መሰረት በማድረግ ደንብ ማውጣት በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ ሕገ – መንግሥት አንቀጽ 55(1) እና በፌደራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት ማቋቋሚያ
(ማሻሻያ) አዋጅ ቁጥር 982/2008 አንቀጽ 22(1) መሠረት ይህ ደንብ ወጥቷል፡፡
•
•
•
•
•
•
•
•
•
•