በሎካ አባይ ወረዳ በመገኘት ማኅበራዊ ድጋፉን ያደረጉት የፍትሕ ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮች ከ4000 በላይ የሚሆኑ የተመረጡ ችግኞችን የተከሉ ሲሆን ለ1000 የአቅመ ደካማ ቤተሰብ ልጆች ደብተር እና እስኪርቢቶዎችን አበርክተዋል።
በተጨማሪም የ3 አቅመ ደካማ ቤቶችን የማሳደስ ስራ አስጀምረዋል።
በማኅበራዊ ድጋፍ መድረኩ ላይ ክቡር የፍትሕ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቴዎስን ጨምሮ ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ ዳይሬክተሮች እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።