አቶ አወል ሱልጣን ጥቅምት ወር 2016 ዓ.ም ጀምሮ በቀድሞው የብሔራዊ የድርጊት መርሃ ግብር ጽ/ቤት ተብሎ የሚጠራውን የብሄራዊ የሰብአዊ መብት ክትትል ዳይሬክቶሬትን እየመሩ ቆይተዋል። በእርሳቸው አመራር የፍትህ ሚኒስቴር የቢዝነስ እና የብሄራዊ የድርጊት መርሃ ግብር ዝግጅት ተጀምሯል። ሁሉን አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መከታተያ ማንዋልን ለማዘጋጀት በትጋት ሰርተዋል። አቶ አወል የመንግስት ሪፖርቶችን በማዘጋጀት እና በተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት አሠራሮች ውስጥ ሀገራዊ ሪፖርቶች ውይይቶች ላይ በአካል ተገኝተው የማቅረብ ስራ ሰርተዋል። 

ኃላፊነት ዘመናቸው የማረሚያ ቤቶችን እና የእስር ቤቶችን በተደራጀ መልኩ በመጎብኘት የታራሚዎች እና የእስረኞች አያያዝ ለማሻሻል ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል። በተጨማሪም የኢፌዲሪ የሽግግር የፍትህ ፖሊሲን ትግበራ በማስተባበር ረገድ አስተዋፅዖ አበርክቷል።

አቶ አወል አሁን ካሉበት የስራ ኃላፊነት በፊት የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና የትምህርት ቡድን መሪ እንዲሁም በክልል እና በፌደራል ደረጃ አቃቤ ህግ በመሆን አገልግለዋል። ጀማሪ አቃቤ ህግ፣ ከፍተኛ አቃቤ ህግ የሚባሉ የዐቃቤ ህግነት ደረጃዎችን አልፈው በአሁኑ ጊዜ ምክትል ረዳት ጠቅላይ ቃቤ ህግ ሆነው በማገልግል ላይ ይገኛሉ፡፡ አቶ አወል በቀደመው የስራ ኃላፊነታቸው በፍትህ ሚኒስቴር የሚገኘውን የፍትህ ሙዚየም በማስጀመር እና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ብራንዲንግ በአዲስ የመተካት ስራ ውስጥ ግንባር ቀደም ነበሩ።

የትምህርት ዳራ

  • ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
  • በሰብዓዊ መብቶች ሕግ ሁለተኛ ዲግሪ