በሥራ ላይ ባለው የጉምሩክ አዋጅ የተዘረጋው የጉምሩክ አሠራር ሥርዓት ከዘመኑ የገቢና ወጭ ንግድ እንቅስቃሴ አፈጻጸም ጋር አብሮ የማይሄድ ስለሆነ የዓለም አቀፉ የሸቀጦች ልውውጥ ከደረሰበት የዕድገት ደረጃ ጋር የሚጣጣም የአሠራር ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፤
የጉምሩክን የአሠራር ሥርዓት የተቀላጠፈና አጭር ለማድረግ የሥራ አመራር ነጻነት ኖሮት እንዲቋቋም ማድረግ ተገቢ መሆኑስለታመነበት፤
የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ ውስብስብ እየሆነና ኃይል እየታከለበት በመምጣቱ ይህንን ለመከላከል የሚያስችል ፖሊሳዊ ሥልጣን ያለው ባለሥልጣን ማደራጀት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።
•
•
•
•
•
•