የሕዝብ ቆጠራ ውጤት የሕዝቡን ኑሮ ለማሻሻል ለሚደረገው ሕገ መንግሥታዊ አደረጃጀትና ለፖለቲካዊ ሥርዓቱ ዝግጅት አስፈላጊ ስለሆነ
ትክክለኛውን የሕዝብ ብዛት ማወቅ በሀገር አቀፍ ወይም በተወሰነ የክልል አስተዳደር እርከን ደረጃ ለሚደረጉ ምርጫዎች አፈጻጸም አስተማማኝ መሠረት በመሆኑ፤
የተግባሩን አስፈላጊነት፣ ስፋት እና ውስብስብነት በማገናዘብ የሕዝብ ቆጠራ ኮሚሽን እንደሚቋቋም በሕገ መንግሥቱ የተደነገገውን በሥራ ላይ ለማዋል ዝርዝር ሕግ ማውጣት አስፈላጊ በመሆኑ፤
የሕዝብ ቆጠራ ኮሚሽንን ለማቋቋም ቀደም ሲል የወጣው አዋጅ ቁጥር 180/1991 በተግባር ሲታይ የሥራ ድግግሞሽን የሚፈጥር ሆኖ በመገኘቱ፣
በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 103103 እና አንቀጽ 55 (1) መሠረት ከዚህ እንደሚከተለው ታውጇል፡፡
•