አብዛኛው በወጪና ገቢ ንግድ የተሰማራው ባለሃብት ታክስ የሚከፍለው ለፌደራል መንግሥት ቢሆንም ከታክስ እንዲሁም ከወጪና ከገቢ ንግድ ጋር የተያያዙ የመንግሥት አገልግሎቶች በተለያዩ ተቋማት እንዲሰጡ መደረጋቸው በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በመረጃ አያያዝና አጠቃቀም እንዲሁም ህግና ስርዓትን በማስክበር ረገድ ችግር ያስከተለ በመሆኑ፤
የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ባለሥልጣን እና የፌደራል አገር ውስጥ ገቢ ባለሥልጣን በተመሳሳይ ዓላማ ላይ ያተኮሩ ከመሆናቸው በላይ ተመሳሳይ የሃብት አጠቃቀምና የአደረጃጀት ስልት የሚከተሉ በመሆናቸው የሦስቱ ተቋማት መዋሃድ ዘመናዊ የታክስና የጉምሩክ አስተዳደር ሥርዓትን ለመዘርጋት፣ የሃብት አጠቃቀምና የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ ስለሚረዳ፤
ተቋማቱን በማዋሃድ የገቢውን ዘርፍ ውጤታማነት ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።
•
•
•
•
•
•
•