የግል ትምህርት ቤቶችን የሕዝብ ሀብት ለማድረግ በወጣው አዋጅ መሠረት የሕዝብ ሀብት የተደረጉትን ትምህርት ቤቶች አመራርና አስተዳደር አግባብ ካላቸው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት አካላት አወቃቀር ጋር እንዲጣጣም ማድረግ በማስፈለጉ፤
የሕዝብ ትምህርት ቤቶች የትምህርት አሰጣጥ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሊኖር የሚገባውን የትምህርት ደረጃ የጠበቀና ትምህርት ቤቶቹ በሚገኙበት ብሔራዊ ክልል ወይም የከተማ መስተዳድር የተዘረጋውን የትምህርት ሥርዓት የተከተለ እንዲሆን በማስፈለጉ፤
በሕዝብ ትምህርት ቤቶች የሚሰጠውን የትምህርት ደረጃ ለማሻሻል የሚያስችል፤ የትምህርት ቤቶቹን መምህራን መብትና ጥቅም የሚያስከብር እንዲሁም ተጠቃሚ የሆነው ኅብረተሰብ የተሻለ አገልግሎት የሚያገኝበት አደረጃጀት እንዲኖር ማድረግ በማስፈለጉ፤
የትምህርት ቤቶችን አመራርና አስተዳደር ለማጠናከር የወጣውን አዋጅ ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55 (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።
•
•
•
•
•
•
•