ለአክሱም ውሃ አቅርቦት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል መጠኑ 6 ሚሊዮን 200 ሺህ የኩዌት ዲናር (ስድስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ የኩዌት ዲናር) የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በኩዌት ፈንድ ለአረብ ኢኮኖሚ ልማት መካከል እ.ኤ.እ ጁን 16 ቀን 2005 በአዲስ አበባ የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 30 ቀን 2007 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስት አንቀፅ 55 (1) እና (12) መሰረት የሚከተለው ታውጃል።
•
•
•
•
•
•
•
•
•
•