በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት፣ በሱዳን ሪፐብሊክ መንግሥት እና በየመን ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል የተደረገው የማሪታይም ጉዳዮች ስምምነት ታህሣሥ 18 ቀን 1997 ዓ.ም ካርቱም ላይ የተፈረመ ስለሆነ፣
ይህንኑ ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 23 ቀን 1997 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፣
በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 55 (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•