ለጅማ-ጭዳ እና ለሶዶ-ሳውላ የመንገድ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል 25 ሚሊዮን 589 ሺ 863 ዩ.ኤ (ሃያ አምስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሰማንያ ዘጠኝ ሺ ስምንት መቶ ስድሳ ሦስት ዩኒትስ ኦፍ አካውንት) የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በአፍሪካ ልማት ፈንድ መካከል ጥር 22 ቀን 2009 ዓ.ም በአዲስ አበባ የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥር 30 ቀን 2009 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55(1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፦
•
•
•
•
•
•
•
•
•
•