ለአነስተኛና መካከለኛ ከተሞች የመጠጥ ውሃ አቅርቦት፣ ሳንቴሽንና መሠረተ ልማት ማስፋፊያና ማሻሻያ ፕሮግራም ከፊል ማስፈጸሚያ የሚውል ፵ ሚሊዮን (አርባ ሚሊዮን) ዩሮ የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ መካከል እ.ኤ.አ. ኖቬምበር 26 ቀን 2015 በአዲስ አበባ እና ዲሴምበር 3 ቀን 2015 በሉክዘምበርግ የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጋቢት 27 ቀን 2008 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግሥቱ አንቀጽ 55 (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፦
•
•
•
•
•
•