የመድሐኒት ምርቶችን በጥራት፣ በጥንቃቄና ውጤታማነቱን በጠበቀ መልኩ ተደራሽ ማድረግ ለሕብረተሰብ ጤና እና ደህንነት መሠረታዊ ጉዳይ በመሆኑ፣
የአፍሪካ ሕብረት የካቲት 4 ቀን 2021 ዓ.ም ባደረገው የኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች መደበኛ ጉባዔ ላይ የአፍሪካ መድሐኒቶች ኤጀንሲን ለማቋቋም የሚያስችለውን ስምምነት የተቀበለው በመሆኑ፣
ስምምነቱ በአፍሪካ መድሐኒቶች ኤጀንሲ መሪነት የህብረቱ አባል ሀገራት በደረጃቸው ጥራት ዝቅ ካሉና ሐሰተኛ ከሆኑ የመድሐኒት ምርቶች ጋር በተያያዘ የሚፈጠሩ አደጋዎችን በመቆጣጠር የህብረተሰባቸውን ጤና በአግባቡ ለመጠበቅ የሚያስችላቸው በመሆኑ፣
ስምምነቱን ማጽደቅ ኢትዮጵያ የመድሐኒት ምርቶችን ለመቆጣጠር በምታደርገው ጥረት ውስጥ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ያለው በመሆኑ፣
ይህንን ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በህዳር 20 ቀን 2016 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ የመረመረውና ያጸደቀው በመሆኑ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•
•