በአገልግሎት ላይ

የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ

ከኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መሠረታዊ ዓላማዎች አንዱ የሆነውን በሕግ የበላይነት ላይ የተመሰረተ አንድ የፖለቲካ ማኅበረሰብ በጋራ የመገንባት ዓላማ ከግብ የሚደርሰው የግለሰብ፣ የብሔር/ብሔረሰብ እና የሕዝብ መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች መከበራቸው ሲረጋገጥ በመሆኑ፤

የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መስፈን እንዲሁም ለኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገቱ መደራጀት ባካሔደው ረጅም ትግል በከፈለው መስዋዕትነት ሰብአዊ መብቶች ለማናቸውም ዓይነት የተፅዕኖ መዳፍ ሳይጋለጡ በእውን የሚከበሩበትን ሁኔታ ማመቻቸት በማስፈለጉ፤

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት የሕዝቦች መብቶችና ነፃነቶች የተከበሩ መሆናቸው በመረጋገጡና በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ የፌደራልና የክልል መንግሥታት አካላትና ባለሥልጣኖቻቸው እነዚህን የማክበርና የማስከበር ኃላፊነትና ግዴታም እንዳለባቸው በመደንገጉ፤

መብቶቹንና ነፃነቶቹን በማስከበሩ ረገድ የላቀ ድርሻ ይኖራቸዋል ከሚባሉት አካላት አንዱ የሆነውን የሰብአዊ መብት ኮሚሽንን ማቋቋምና ሥልጣኑንና ተግባሩንም ከሕገ መንግሥቱ ድንጋጌዎች ጋር በሚስማማ መልክ በሕግ መወሰን አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55 (1) እና (14) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF
መለያ: አዋጅ ቁጥር 210/1992
ቀን: ሰኔ 27፥ 1992 ዓ.ም.
Law Type: Proclamations

ሕጉን ያውርዱ

ተዛማጅ ሕጎች

583/2018

ጥር 20÷ 2018 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
1353/2017

ጥር 02÷ 2017 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1370/2017

መጋቢት 9፥ 2017 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1353/2016

ጥር 2፥ 2017 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1353/2016

ኅዳር 10÷ 2016 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1284/2015

ሚያዚያ 9፥ 2015 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
ደንብ ቁጥር 502/2014

መጋቢት 28፥ 2014 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1234/2013

ሚያዚያ 18፥ 2013 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ 1238/2013

መጋቢት 27፥ 2013 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1179/2012

መጋቢት 15፥ 2012 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ