በፍትሕ ሚኒስቴር የሴቶች ሕፃናትና ባለብዙ ዘርፍ ዳይሬክቶሬት በስርዓተ ጾታ አካቶ ትግበራ ዙሪያ ለተቋሙ የአስተዳደር ሰራተኞች በሁለት ዙር በቢሾፍቱ ከተማ ሲሰጥ የነበረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተጠናቋል።
የሴቶች ሕፃናትና ባለብዙ ዘርፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ዳግማዊት አላምኔ እንዳሉት የሥልጠናው ዓላማ በፍትሕ ዘርፍ የሴቶችን ፤ሕፃናትን ፤ወጣቶችን ፤አካል ጉዳቶችንና አረጋዊያንን አካቶ ለመተግበር እና የተሳትፎ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በአካቶ ትግበራ ዙሪያ ለተቋሙ አስተዳደር ሰራተኖች ግንዛቤ ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ተናግረዋል።
አያይዘውም የስራ ክፍሉ የሴቶችና ህጻናት እንዲሁም ባለብዙ ዘርፍ ጉዳዮች ተካተው መተግበራቸውን የመከታተል ዋነኛ ኃላፊነት የተሰጠው መሆኑን አንስተው፣ ሥልጠናው የተቋሙ ሰራተኞች አካቶ ከመተግበር አንፃር እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን መነሻ በማድረግ የኦዲት ጥናት ተካሂዶ በጥናቱ ግኝት መነሻነት የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በሥልጠናው የአካቶ ትግበራ ምንነት እና ዋና ዋና ጉዳዮች፤ የማካተት አስፈላጊነት የማካተት ስልቶች፤ የማካተት ደረጃ ፤ለአካቶ ትግበራ ምላሽ ሰጪ ተቋማት ባህሪያት የስርዓተ ጾታ ዋና ዋና ጉዳዮች እና የሕግና የፖሊሲ ማዕቀፎች የሚሉት ተዳሰውበታል ፡፡
ሥልጠናውን ተከትሎ በተሳታፊዎች ለቀረቡ ሀሳብ አሰተያየቶች በአሰልጣኞች አማካኝነት ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት የግንዛቤ ማስጨበጫ የሥልጠና መድረኩ ተጠናቋል፡፡