በድሬዳዋ አስተዳደር በህዝብ የተመረጠ ምክር ቤት እስኪመሰረት ድረስ በጊዜያዊ አስተዳደር እንዲመራ በሕግ የተደነገገ በመሆኑ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር ቻርተር አዋጅን ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 413/1998 ዓ.ም መሠረትም የጊዜያዊ አስተዳደሩ የሥራ ጊዜ የሚጠናቀቀው ታህሣሥ 26 ቀን 1999ዓ.ም በመሆኑ፤
የአስተዳደሩን የምክር ቤት ምርጫ ለማካሄድ የሚያስፈልጉ ቅድመ ዝግጅቶች ያልተጠናቀቁ በመሆናቸው እና ይህንንም ምርጫ የጊዜያዊ አስተዳደሩ የሥራ ጊዜ ከመጠናቀቁ በፊት ማከናወን ባለመቻሉ፤
የድሬዳዋ አስተዳደር የምክር ቤት ምርጫ እስከ ሚከናወን ድረስ የአስተዳደር ክፍተት እንዳይፈጠር ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ- መንግሥት አንቀፅ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•
•