በምርምር የተገኙ አዳዲስ የዕፅዋት ዝርያዎችን መጠቀም የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያበረክት በመሆኑ፣
አዳዲስ የዕፅዋት ዝርያዎችን በምርምር አዳቅሎ ማውጣት ከፍተኛ ጥራትና መዋዕለ ነዋይ የሚጠይቅ በመሆኑ፣
አዳዲስ የዕፅዋት ዝርያዎችን በምርምር አዳቅሎ በማውጣት ሥራ ላይየተሰማሩ ሰዎች በመስኩ የሚያደርጉትን ጥረትና ኢንቨስትመንት ለማበረታታት ለሥራቸው ውጤት እውቅና መስጠትና የኢኮኖሚ ጥቅም እንዲያገኙበት ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፣
የዕዕዋት አዳቃዮችን መብት ከማበረታታት ጐን ለጐን አዳዲስ የዕዕዋት ዝርያን በማውጣት ግብዓት የሆነውን የዕዕዋት ጀነቲክ ሀብት ጠብቀው ያቆዩትና ወደፊትም የሚጠብቁት የአገራችን አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች ዘርን የመጠቀምና መለዋወጥ ለዘመናት የቆየው ልማዳዊ ሥርዓታቸው እንዲቀጥል ማድረግ አስፈላጊና ተገቢ በመሆኑ፣
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክሕገ መንግሥት አንቀጽ 55 (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል::
•
•
•
•
•
•
•
•
•