በአገልግሎት ላይ

ለቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ብድር ከዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ለማግኘት የተፈረመው የብድር ስምምነት ማፅደቂያ አዋጅ

ለቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል 65 ሚሊዮን 330 ሺህ ኤስ.ዲ.አር (ስልሳ አምስት ሚሊዮን ሦስት መቶ ሰላሳ ሺህ ኤስ.ዲ.አር) የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ መካከል እ.ኤ.አ ኖቬምበር 19 ቀን 2019 በሮም የተፈረመ በመሆኑ፤

ይህንኑ ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሚያዚያ 22 ቀን 2012 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፤

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀጽ 55(1) እና (12) መሠረት የሚሜከተለው ታውጇል፡፡

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF
መለያ: አዋጅ ቁጥር 1196/2012
ቀን: ግንቦት 13፥ 2012 ዓ.ም.
Law Type: Proclamations

ሕጉን ያውርዱ

ተዛማጅ ሕጎች