ለመጠጥ ውሃ፣ ሳኒቴሽንና ሃይጅን ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል መጠኑ 133 ሚሊዮን 200 ሺህ ኤስ.ዲ.አር (አንድ መቶ ሠላሳ ሦስት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ ኤስ.ዲ.አር) የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በዓለም አቀፍ የልማት ማህበር መካከል እ.አ.አ. ኤፕሪል 10 ቀን 2014 በአዲስ አበባ የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 55 (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•