አገር ዓቀፍ የጤና መመዘኛ መስፈርቶችን በማዉጣት እና በመተግበር ተጠያቂነትና ጥራት ያለው እንዲሁም ተደራሽ የሆነ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፤
የአገሪቱ የጤና አገልግሎት በማዘመን የሕብረተሰቡን የጤና ፍላጎት ለማሟላት የሚያስችል አሰራር መዘርጋት በማስፈለጉ፤
የአገሪቱን የጤናና ጤና ተቋማት እና ባለሙያዎች እንዲሁም ጤና ነክ ተቋማት ቁጥጥር ሥርዓት ቀልጣፋ ዉጤታማና ወጥነት ያለው እንዲሁም የሕግ ማሻሻያዎችን ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
የጤና አገልግሎት ሥርዓቱን ለማሻሻል የሚካሄዱ የጥናትና ምርምር ሥራዎች የሚመሩበት እና የሚተገበሩበት አሰራርን መዘርጋት በማስፈለጉ፤
የጤና መረጃ ሥርዓት በመዘርጋት በመረጃ ላይ የተመሰረተ ዉሳኔ አሰጣጥ በማረጋገጥ የቴና እና ጤና ነክ አገልግሎት ጥራት፤ ደህንነት፤ ፍትሃዊነት ተደራሽነት እና የተገልጋይ ደኅንነት ማሻሻል በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታዉጇል፡፡
•
•
•
•
•
•
•
•