የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የተቋቋመበትን ዓላማ ለማሳካት የምርት ገበያውን ተደራሽነት የበለጠ በማስፋት የግብይት ተዋናዮችን ፍላጎትና አነስተኛ አምርቾች በገበያው ያላተቸውን ተሳትፎ ማሳደግ የሚያስችል አሰራር መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ፣
የግብርና ምርቶች በዓይነት በመጠንም ሆነ በጥራት ወጪ ቆጣቢ በሆነ ሁኔታ ወደ ምርት ገበያው የሚቀርቡበትን አመቺ ሁኔታ በመፍጠር በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በማድረግ የአገሪቱን የውጭ ንግድ በማጠናከር የምርት ገበያውን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 550/1999 ን እንደገና ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀጽ 55 (1) መሰረት እንደሚከተለው ታውጇል;-
•
•
•
•
•
•
•
•