በአገልግሎት ላይ

ለመቀሌ ውሃ አገልግሎት አቅርቦት ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል ብድር ከቻይና ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ ለማግኘት የተፈረመውን የብድር ስምምነት ማፅደቂያ አዋጅ

ለመቀሌ ውሃ አገልግሎት አቅርቦት ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል 1 ቢሊዮን 70 ሚሊዮን ሪንሚንቢ ዩዋን (አንድ ቢሊዮን ሰባ ሚሊዮን ሪንሚንቢ ዩዋን) ኮንሴሽናል ብድር የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በቻይና ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ መካከል ሰኔ 6 ቀን 2010 ዓ.ም በቤጂንግ የተፈረመ በመሆኑ፤

እንዲሁም ለዚሁ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል 540 ሚሊዮን ሪንሚንቢ ዩዋን (አምስት መቶ አርባ ሚሊዮን ሪንሚንቢ ዩዋን) በቻይና ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ በኩል የሚቀርብ ከወለድ ነፃ የሆነ የማዕቀፍ የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በቻይና ሕዝባዊ ሪፐብሊክ መንግስት መካከል ግንቦት 2 ቀን 2010 ዓ.ም በአዲስ አበባ የተፈረመ በመሆኑ፤

ይህንኑ ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጋቢት 27 ቀን 2011 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፣

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀጽ 55 (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡-

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF
መለያ: አዋጅ ቁጥር 1137/2011
ቀን: ሚያዚያ 10፥ 2011 ዓ.ም.
Law Type: Proclamations

ሕጉን ያውርዱ

ተዛማጅ ሕጎች

አዋጅ ቁጥር 1301/2016

ታህሳስ 10፥ 2016 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ