ጤና ለሕዝብ የተደላደለ ሕይወትና ምርታማነት መሠረት መሆኑንና መድኃኒትም በጤና አገልግሎት ውስጥ ያለውን ድርሻ እንዲሁም ጤና ለእንስሳት ምርትና ምርታማነት ብሎም ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚያስገኘውን ጠቀሜታ በመገንዘብ፤
የመድኃኒት ደህንነት፡ ፈዋሽነትና ጥራት ማረጋገጥና ምርቱን፥ ሥርጭቱን፡ አጠቃቀሙን ሥርዓት ማስያዝ በማስፈለጉ፤
የናርኮቲክና ሣይኮትሮፒክ መድኃኒቶችን ሕገወጥ ምርት፡ ሥርጭትና አጠቃቀም መግታት በማስፈለጉ፥
ለዚህም አስተማማኝ የሆነ የመድኃኒት አስተዳደርና ቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገመን ግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።
•
•
•
•
•
•
•