ለክብረመንግሥት ከተማ የውኃ አቅርቦት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል መጠኑ 6 ሚሊዮን 240 ሺ የአሜሪካን ዶላር (ስድስት ሚሊዮን ሁለት መቶ አርባ ሺህ የአሜሪካን ዶላር) የሚያስገው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በአረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት መካከል እ.ኤ.አ. ጁላይ 9 ቀን 2004 በአዲስ አበባ ከተማ የተፈረመ በመሆኑ፤
መሠረታዊ የኤኮኖሚ ዓለም ዐቀፍ ውሎች ተፈፃሚ ከመሆናቸው በፊት መፅደቅ ስላለባቸው፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥቅምት 23 ቀን 1997 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው ስለሆነ፤
በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•