የኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥትና የቱኒዚያ ሪፐብሊክ መንግሥት በእኩልነትና በጋራ ጥቅም ላይ በተመሠረተ አኳኋን በሁለቱ ሀገሮች መካከል የንግድ ሥራ ለማካሄድና ለማስፋፋት በዚሁም አማካይነት የኢኮኖሚ ግንኙነቶችን ለማጎልበት ባላቸው ፍላጎት መነሻ በቱኒዚያ ሪፐብሊክ ዋና ከተማ በቱኒዝ ጥቅምት 24 ቀን 1987 የንግድ ስምምነት በመፈራረማቸው፤
ስምምነቱ በሚገባ ሥራ ላይ የሚውለው በተዋዋዮቹ ሀገሮች ሕጎች መሠረት ስምምነቱ መጽደቁን ከሚያረጋግጡ ሰነዶች ልውውጥ በኋላ እንደሚሆን በስምምነቱ ውስጥ በመመልከቱ፤
ይህንኑ ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የካቲት 5 ቀን 1988 ባደረገው ስብሰባ ያጸደቀው ስለሆነ፤
በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ (1) እና (12) መሠረት ከዚህ እንደሚከተለው ታውጇል።
•
•
•
•
•
•
•
•