የሎተሪ ሥራ ከጊዜ ወደ ጊዜ በዓይነትና በአጨዋወት ዘዴው እያደገና እየሰፋ በመምጣቱ ምክንያት በተጠናከረና ሥርዓት ባለው መንገድ ለማካሄድ፣ ለመምራትና ለመቆጣጠር እንዲቻል እንዲሁም ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ ለኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት የሚያደርገው እገዛ የተሻለ እንዲሆን ለማስቻል የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደርን ድርጅታዊ አቋም ማሻሻልና ማጠናከር በማስፈለጉ፤
የግሉን ክፍለ ኢኮኖሚ በሎተሪ ሥራ ላይ እንዲሳተፍ ማድረጉ የዘርፉን የአገልግሎት ብቃት ከፍ ለማድረግ ያስችላል ተብሎ በመታመኑ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•
•