በመንግሥት እና በግሉ ዘርፍ ዓለም እቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት እና የኦዲት ደረጃዎች እንዲተገበሩ መንግሥት የወሰነ በመሆኑ ይህንን ለማስፈጸም በቂ እና ብቁ የተመሠከረላቸው የሒሣብ ባለሙያዎች ማፍራት በማስፈለጉ፤
የተመሠከረላቸው የሒሣብ ባለሙያዎች ለማፍራት እና ሙያውን ለማሳደግ ተቋም ማቋቋም በማስፈለጉ፤
የሒሣብ ሙያን እና የሒሣብ ባለሙያን በሀገር እና በዓለም ኣቀፍ ደረጃ የሚወክል ተቀም በማስፈለጉ፤
የሕዝብ ጥቅምን ለማስጠበቅ የሒሣብ ሙያን እና የሙያተኛውን አቅም ማሳደግ በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ (ሐ) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•