የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 398/2009 የተቋቋመና ከኮርፖሬሽኑ ተልዕኮ አንጻር የተለያዩ ዓላማዎች የኮርፖሬሽኑ ቤቶች የኪራይ ተመን እንዲዘጋጅ ኃላፊነት የተሰጠው በመሆኑ፣
የኮርፖሬሽኑ ቤቶች ኪራይ ተመን ከግል ዘርፍ የኪራይ ተመን አንጻር ሲታይ እጅግ በጣም የተራራቀ (የኮርፖሬሽኑ የኪራይ ተመን በጣም ያነሰ) በመሆኑ የንግድ ስርዓቱ ላይ ክፍተት በመፍጠሩ፣ የሃብት ክፍፍለ\ል ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ በማሳደሩና የግብር ስርዓቱን እያዛባ ስለሚገኝ የሁለንም አካል ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የኪራይ ተመኑን ማሻሻል አስፈላጊ በመሆኑ፣
ኮርፖሬሽኑ ከተሰጠው መጠነ-ሰፊ ተልዕኮ አንጻር ኃላፊነቱን የመወጣት፣ የገቢውን መጠን ለማሳደግና የኮርፖሬሽኑን ህሌውና ቀጣይነት ለማረጋገጥ የነበረውን የኪራይ ተመን ስርዓት በማሻሻል ማዘጋጀት አስፈላጊ በመሆኑ፣
ኮርፖሬሽኑ የሚከራያቸውን ቤቶች ኪራይ ተመን ሲያዘጋጅ ግልፅና ተጠያቂነት ያለው ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፣
የኮርፖሬሽኑ ሥራ አመራር ቦርድ በመንግሥት የልማት ድርጅቶች አዋጅ 25/1984 አንቀጽ 14(4) መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡