የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ዘሬ በሸራተን አዲስ ባካሄደው የዕውቅና መርሃ ግብር በሕግ ማስከበር ዘመቻው ለበረከቱና እና በስራ አፈፃፀም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ የተቋሙ አመራሮችና አባላት እውቅናና የማዕረግ እድገት ሰጥቷል፡፡
በመረሃ ግብሩም ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮ/ር ደራርቱ ቱሉና በርካታ ጀግኖች አትሌቶችን ላፈሩት አንጋፋው አሰልጣኝ ኮ/ር ሁሴን ሼቦ የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረግ ሰጥቷል፡፡
በመርሃግብሩ ላይ የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ተገኝተው የረዳት ኮሚሽነርነት ማዕረጉን በማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል ዳመና ዳሮታ አቅራቢነት ሰጥተዋል፡፡በመድረኩ በኢፌዲሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕ እና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ሰብሳቢ ወ/ሮ እጸገነት መንግሥቱ፣ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ፣ የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስትር ዶ/ር አብርሃም በላይ እና ሌሎችም ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል::