መንግስት ሕገ መንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ሥርዓቱን ከአደጋ የመከላከልና የመጠበቅ፣ የሀገርን ሰላምና ደህንነት የማስከበር እና የህዝቦችን አንድነትና እኩልነት እውን በማድረግ የዜጎች በነፃነት የመዘዋወር፣ በመረጡት ቦታ የመኖርና ሀብት የማፍራት ህገመንግስታዊ መብታቸውን የመጠበቅ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን በመገንዘብ፤
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገራችን አንዳንድ አካባቢዎች ሕገ መንግስቱን እና ሕገ መንግስታዊ ሥርዓቱን፣ የህዝብን ሰላምና ደህንነት የሚጥስና ለአደጋ የሚያጋልጥ ብሎም የህዝቦች በአንድነት አብሮ የመኖር እሴትን የሚንድ፣ የመንግስትና የግሉ ዘርፍ የስራ እንቅስቃሴን የሚያስተጓጉል፣ የህግ የበላይነትን የሚያዳክም፣ በምትኩ ደግሞ በሀይል የታገዘ ሁከትና ብጥብጥ እንዲሁም ሥርዓት አልበኝነትን የሚያነግስ፣ የበርካታ ንፁሀን ሰዎችን ህይወት ያጠፋና ብሄርን መሰረት ያደረገ ጥቃት እየተፈፀመና የህዝቦች መፈናቀል እየደረሰ፣ የሀገራችን ኢኮኖሚ እየተጎዳ፣ ንብረት እየወደመ፣ የህዝቡ በሰላም ወጥቶ መግባት እየታወከ እንዲሁም ይህ ሁኔታ እየተስፋፋና እየተራዘመ መሄዱን በመገንዘብ፤
•
•