በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥትና በስፔን ንጉሣዊ መንግሥት መካከል ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና ዋስትና ለመስጠት የባለ-ሁለት ወገን ስምምነት መጋቢት 8 ቀን 2001 ዓ.ም በማድሪድ የተፈረመ ስለሆነ፣
ስምምነቱ ሥራ ላይ የሚውለው በተዋዋዮቹ ሀገሮች ሕግ መሠረት መጽደቁን የሚያረጋግጡ ሰነዶች በዲፕሎማቲክ አካላት አማካኝነት ልውውጥ ከተደረገ ከ30 ቀን በኋላ እንደሆነ በስምምነቱ ስለተገለጸ፤
ይህንኑ ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 23 ቀን 2001 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው ስለሆነ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።
•
•
•