የአየር አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ስምምነት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት እና በቱኒዚያ ሪፐብሊክ መንግሥት መካከል እ.ኤ.አ. ጃንዋሪ 23 ቀን 2003 በቱኒስ የተፈረመ በመሆኑ፤
ስምምነቱ በሥራ ላይ የሚውለው በሁለቱ ተዋዋይ ሀገሮች ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት መሠረት ስምምነቱ መጽደቁን የሚያረጋግጡ የዲፕሎማቲክ ሰነዶች ልውውጥ ከሚደረግበት ዕለት ጀምሮ እንደሚሆን በስምምነቱ ውስጥ የተመለከተ በመሆኑ፤
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 18 ቀን 2001 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያጸደቀው ስለሆነ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ- መንግሥት አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀፅ (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•