ለገጠር የፋይናንስ ሥርዓት ማስፋፊያ ሁለተኛ ፕሮግራም ማስፈጸሚያ የሚውል መጠኑ ኤስ.ዲ.አር. 31 ሚሊዮን 300 ሺ (ሰላሳ አንድ ሚሊዮን ሶስት መቶ ሺ ኤስ.ዲ.አር.) የሆነ ገንዘብ የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ መካከል እ.አ.አ. ዲሴምበር 21 ቀን 2011 በሮም የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሚያዝያ 30 ቀን 2004 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•