ለጅጅጋ-ደገሐቡር አካባቢዎች ገጠር ኤሌክትሪክ ሥርጭት ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል መጠኑ 20 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር (ሃያ ሚሊዮን የአሜሪካ የአሜሪካ ዶላር) የሚያስገኘው ብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በኦፔክ ፈንድ ለዓለም አቀፍ ልማት መካከል እ.ኤ.አ ጁላይ 7 ቀን 2010 በቪየና የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ጥር 3 ቀን 2003 ዓ.ም ባካሔደው ስብሰባ ያፀደቀው ስለሆነ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡