የተሻረ

በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ውስጥ ለተሳተፉ ሰዎች ምህረት ለመስጠት የወጣ አዋጅ

በሀገራችን ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈንና እየተካሄደ ያለውን ለውጥ ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ ለማድረግ ተከስቶ የነበረውን ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ተከትሎ በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ውስጥ የተሳተፉ ሰዎች ለድርጊታቸው የወንጀል ተጠያቂነታቸውን በጠቅላላው በመሰረዝ ወደ ሕብረተሰቡ ተቀላቅለው በሀገር ግንባታ ውስጥ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፤

በሀገራችን የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታን ለማሳደግና የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ፖለቲካዊ መብታቸውን ተግባራዊ ለማድረግ በመንቀሳቀሳቸው ምክንያት የወንጀል ተጠያቂነት ሊያስከትል ይችላል በሚል ስጋት በተለያዩ የዓለም አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ምህረት በመስጠት ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ሁኔታዎችን ማመቻቸት በማሰፈለጉ፤

የጥላቻና የእርስ በእርስ ጥርጣሬን በማስወገድ በመፈቃቀድና በአንድነት የተጀመረውን የሀገራችን ማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠርና ይቅር መባባል አስፈላጊ በመሆኑ፤

በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀጽ 55 (1) መሰረት የሚከተለው ታውጇል።

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF
መለያ: አዋጅ ቁጥር 1096/2018
ቀን: ጷጉሜ 2፥ 2010 ዓ.ም.
Law Type: Proclamations

ሕጉን ያውርዱ

ተዛማጅ ሕጎች

589/2018

ሚያዝያ 20÷2018 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ

በአገልግሎት ላይ
1401/2018

ሚያዝያ 13÷2018 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
1401/2018

ሚያዝያ 13÷2018 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ