በሀገራችን ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈንና እየተካሄደ ያለውን ለውጥ ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ ለማድረግ ተከስቶ የነበረውን ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ተከትሎ በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች ውስጥ የተሳተፉ ሰዎች ለድርጊታቸው የወንጀል ተጠያቂነታቸውን በጠቅላላው በመሰረዝ ወደ ሕብረተሰቡ ተቀላቅለው በሀገር ግንባታ ውስጥ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲያበረክቱ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
በሀገራችን የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታን ለማሳደግና የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ፖለቲካዊ መብታቸውን ተግባራዊ ለማድረግ በመንቀሳቀሳቸው ምክንያት የወንጀል ተጠያቂነት ሊያስከትል ይችላል በሚል ስጋት በተለያዩ የዓለም አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ምህረት በመስጠት ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ሁኔታዎችን ማመቻቸት በማሰፈለጉ፤
የጥላቻና የእርስ በእርስ ጥርጣሬን በማስወገድ በመፈቃቀድና በአንድነት የተጀመረውን የሀገራችን ማሕበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠርና ይቅር መባባል አስፈላጊ በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀጽ 55 (1) መሰረት የሚከተለው ታውጇል።
•
•