ደህንነቱ ባልተጠበቀ ምግብ ምክንያት በኅብረተሰቡ ላይ ሊደርስ የሚችለውን የጤና ጉዳት መከላከል እና መቆጣጣር አስፈላጊ በመሆኑ፤
ደህንነቱ፣ ፈዋሽነቱና ጥራቱ ባልተረጋገጠ መድኃኒት እንዲሁም ደህንነቱ እና ውጤታማነቱ ባልተረጋገጠ የህክምና መሣሪያ ምክንያት በሰው ላይ የሚደርስን የጤና ችግር መከላከል እና መቆጣጣር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
የናርኮቲክና የሳይኮትሮፒክ መድኃኒቶችንና እነዚህ ምርቶች ለማምረት የሚያገልግሉ የፕሪከርሰር
ኬሚካሎችን ሕገ-ወጥ ሥርጭትና አጠቃቀም መከላከልና መቆጣጠር በማስፈለጉ፤
በትምባሆ ምርት ምክንያት በኅብረተሰብ ላይ እየደረሰ ያለውን የጤና፣ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን መከላከል እና መቆጣጠር አስፈላጊ በመሆኑ፤ የመድኃኒት፣ የህክምና መሣሪያ፣ ሀገራዊ የምግብ፣የውበት መጠበቂያ እና የትምባሆ ምርት አስተዳደር ሥርዓት ለመዘርጋት የሚያስችልየህግ ማዕቀፍ በማስፈለጉ፤
የኢንደስትሪ እና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ቴክኖሎጂ መስፋፋት ጋር የሚጣጣም የቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል:-
•
•
•
•
•
•
•
•
•
•