በአገልግሎት ላይ

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የንግድ ሕግ አዋጅ

የኢኮኖሚ እድገትን እና የሕዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ለንግድ ሥራ ጽኑ የሕግ መሠረት መጣል የግድ ይላል፡፡ በ 1922 ዓ.ም የወጣው የኢትዮጵያ የንግድ ሕግ ለዚህ ዓላማ ከግብ መድረስ አስፈላጊውን መደላድል የሚያኖር ነበር፡፡ ከዘመኑ የኢትዮጵያ የዕድገት ደረጃ አኳያ ሲታይ ከጊዜው እጅግ የቀደመ ነበር ማለትም ይቻላል፡፡

ሆኖም ሕጉ ከወጣበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ስልሳ ዓመታት ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል፡፡ ንግድ እና የመዋዕለንዋይ ፍሰት እጅግ ከመጨመራቸውም በላይ እያደር ድንበር ዘለል ባህሪ እየተላበሱ መጥተዋል፡፡ እነዚህ ክስተቶች በተለይ ኢትዮጵያ ገበያ መር ሥርዓት መከተል ከጀመረችበት ጊዜ ጀምሮ ሕጉ በተግባር እንዲፈተሸ ዕድል ፈጥረዋል፡፡

በመሆኑም ሕጉ ውስጥ አንዳንድ ክፍተቶች እና ጉድለቶች ታይተዋል፡፡ ለአፈጻጸም የማይመቹ እና ለተለያዩ ትርጉሞች የተጋለጡ ብዙ ድንጋጌዎች እንዳሉበትም ግልጽ ሆኗል፡፡ በአጭሩ ለመጪዎቹ አስርት ዓመታት የንግድ እንቅስቃሴን ለመምራትና ለመግዛት ቀርቶ ዛሬ ኢትዮጵያ ለደረሰችበት የኢኮኖሚ እንቅስቀሴ ደረጃም ቢሆን ሕጉ የተሟላ እና በቂ ሆኖ አልተገኘም፡፡

ስለዚህ የነጋዴዎችን፣ የባለሀብቶችን እና በሕጉ ጥቅማቸው በቀጥታ የሚነካ ባለድርሻ አካላት መብቶችን በሚዛናዊ ሁኔታ ለማስተናገድ ፤ የኢትዮጵያን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት በማረጋገጥ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ለማስፋፋት ብሎም የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሳደግ የንግድ ሕጉን ዘመናዊ ማድረግ የግድ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

በመሆኑም በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ (4) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF
መለያ: አዋጅ ቁጥር 1243/2013
ቀን: ሚያዝያ 4፥ 2013 ዓ.ም.
Law Type: Proclamations

ሕጉን ያውርዱ

ተዛማጅ ሕጎች

1360/2017

መጋቢት 03÷ 2017 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1360/2017

መጋቢት 3÷ 2017 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1342/2016

ነሐሴ 8÷ 2016 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
ደንብ ቁጥር 538/2015

ነሐሴ 24፥ 2015 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
ደንብ ቁጥር 526/2015

ኅዳር 19፥ 2015 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
ደንብ ቁጥር 461/2012

ጥር 12፥ 2012 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1163/2012

ታህሣሥ 30፥ 2012 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 1152/2011

ነሐሴ 3፥ 2011 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
ደንብ ቁጥር 392/2009

ህዳር 29፥ 2009 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
አዋጅ ቁጥር 980/2008

ሐምሌ 29፥ 2008 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ