የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የተቋቋመበትን የሰብዓዊ መብቶችን ግንዛቤ የማስፋፋት፣ የማስጠበቅ እና የማስከበር ሥራ በተገቢው መንገድ እንዲያከናውን ማስቻል እና የማስፈጸም አቅሙን ማሳደግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
ለዚህም ይረዳ ዘንድ የኮሚሽነሮች አመራረጥ እና አሿሿም አሳታፊና ግልጽ ማድረግና የኮሚሽኑን የመዋቅር፣ የሠራተኛ ቅጥርና አስተዳደር እንዲሁም የበጀት ነፃነት ማረጋገጥን የሚመለከቱ ድንጋጌዎችን ማሻሻልና የተቋሙን ተዓማኒነት፣ ተቀባይነት እና ውጤታማነት ማጐልበት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 (1) እና 55 (14) መሠረት የሚከተለው ማሻሻያ ታውጇል፡፡
•
•