በነፃ ገበያ የኢኮኖሚ ፖሊሲ መሠረት ለማናቸውም የንግድ ሥራ መስክ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር አስፈላጊ ስለሆነ፤
የንግድ ምዝገባ አፈጻጸምና የንግድ ሥራ ፈቃድ አሰጣጥ ስርዓት የነፃ ገበያ ኢኮኖሚን ለማራመድና ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማስገኘት በሚያስችል መልኩ እንዲሻሻል ማድረግና ሕጋዊ ሆኖ የተሰማራው የንግዱ ሕብረተሰብ በዚህ ረገድ የሚያጋጥሙትን መሰናክሎች ለማስወገድ ተገቢውን ክትትል ለማድረግ፣የንግዱ ሕብረተሰብ ከመንግሥት ሊያገኝ የሚገባውን አገልግሎት ለማቀላጠፍና የአገልግሎት አሰጣጡ ኢኮኖሚያዊ እድገትን እንዲያስገኝ የአሰራር ማሻሻያ ማድረግ በማስፈለጉ፤
የንግድ ምዝገባ ክንውንን እና የንግድ ፈቃድ አሰጣጥን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲደገፍ በማድረግ ለመረጃ አያያዝ አመቺ እንዲሆንና ህገወጥ እንቅስቃሴን ለመግታት እንዲቻል አለምአቀፍ የንግድ ሥራ አመዳደቦችን በመከተልና አስፈላጊ መስፈርቶችን በማስቀመጥ የክትትል ስርአት መዘርጋት በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞከራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገመንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•
•
•