በአገልግሎት ላይ

ለአፍሪካ የንግድ ኢንሹራንስ ኤጀንሲ የአባልነት ክፍያ እንዲውል ከአፍሪካ ልማት ፈንድ የተገኘው ብድር ስምምነት ማጽደቂያ አዋጅ

ለአፍሪካ የንግድ ኢንሹራንስ ኤጀንሲ የአባልነት ክፍያ የሚውል መጠኑ 4 ሚሊዮን 970 ሺ ዩ.ኤ( አራት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰባ ሺ ዩኒትስ ኦፍ አካውንት) ብድር የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ እና በአፍሪካ ልማት ፈንድ መካከል እ.ኤ.አ. ኖቬምበር 30 ቀን 2015 በአዲስ አበባ የተፈረመ በመሆኑ፤

ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጋቢት 27 ቀን 2008 ባደረገው ስብሰባ ያጸደቀው በመሆኑ፤

በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 55 (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፦

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF
መለያ: አዋጅ ቁጥር 939/2008
ቀን: ሚያዚያ 19፥ 2008 ዓ.ም.
Law Type: Proclamations

ሕጉን ያውርዱ

ተዛማጅ ሕጎች