የገጠሩ ሕብረተሰብ መሰረታዊ የሆኑ መኀበራዊ የማግኘት በሩ እንዲከፈትለትና ኢኮኖሚያዊ መሰረተ ልማቶችና አገልግሎቶች ተዘርግተዉለት ገቢዉን ማሳደግ አንዲችል መርዳት አስፋላጊ በመሆኑ፤
ይህ ዓላማ ግብ አንዲመታ በሙከራ መልክ ተቋቁሞ የነበረዉን የኢትዮጵያ መኅበራዊ ተሃድሶ ፈንድ ወደ አገር ዓቀፍ ፕሮግራም ደረጃ ማስፋፋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
ይህን ፕሮግራም ሥራ ላይ ለማዋልና ፕሮጄክቶችን በማመንጨት በመቅረፅና ተግባራዊ በማድረግ ረገድ ከታች ወደ ላይ የአሰራር ስልትን በመከተል ለመስራት የሚችል የማኔጅመንት አካል መፍጠር አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀፅ 55 (1) መሰረት የሚከተለው ተዉጇል፡፡
•
•