በኢትዮጵያ – በሚገኙ የተለያዩ የፖለቲካ እና የሃሳብ መሪዎች እንዲሁም የኅብረተሰብ ክፍሎች መካከል እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አለመግባባት የሚታይ በመሆኑ፣
የሃሳብ ልዩነት እና ይህንን ልዩነት እና አለመግባባት ለመፍታት ሰፋፊ ሀገራዊ የሕዝብ ምክክሮችን አካታች በሆነ መንገድ በማካሄድ ሀገራዊ መግባባት መፍጠር አስፈላጊ በመሆኑ፤
እጅግ መሠረታዊ በሆኑ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ አካታች ሀገራዊ ምክሮችን ማካሄድ የተሻለ ሀገራዊ መግባባትን ለመገንባት፣ በሂደትም የመተማመንን እና ተቀራርቦ የመሥራት ባህልን ለማጎልበት እንዲሁም የተሸረሸሩ ማህበራዊ እሴቶችን ለማደስ ጠቃሚ በመሆኑ ሀገራዊ የምክክር ሂደትን ለማሳለጥ የሚያስችል ሥርዓት በሕግ መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ
ሀገራዊ ምክክሮች ተቀባይነት እና ተዓማኒነት ያላቸው እንዲሆኑ ከሚያስችላቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ ምክክሮቹን የሚያመቻቸውና የሚመራው አካል ብቃትና ገለልተኝነት በመሆኑ፤ ምክሮቹን በብቃትና በገለልተኝነት ለመምራትና ለማስተባበር የሚችል ሰፊ ቅቡልነት ያለው ተቋም ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራስያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታዉጇል።
•
•
•
•
•
•
•
•
•