የጤና አገልግሎት ሽፋን መስፋፋት ለአገሪቱ የተቀላጠፈ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ ድርሻ ያለው መሆኑን በመገንዘብ፤
ሁሉን አቀፍ የሆነ የጤና ሽፋንን ለማረጋገጥ በመንግሥትና በተጠቃሚው ኅብረተሰብ መካከል ወጪን መጋራት ወሳኝ ሆኖ በመገኘቱ፤
የማኅበራዊ ጤና መድህን በአባላት መካከል መደጋገፍን በመፍጠር ፍትሃዊና የተሻለ የጤና አገልግሎትን ለማጎልበት የሚረዳ ቀጣይነት ያለው የጤና ፋይናንስ ማሰባሰቢያ ስልት በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55 ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•
•
•
•